በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት አዘጋጅነት ‹‹Public Diplomacy for Global Cooperation›› በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ፣ ጅቡቲና አፍሪካ ኅብረት የኢንዶኔዢያ አምባሳደር አል ቡስራ ባስኑር (Al Busyra Basnur) መጋቢት 15/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ተገኝተው ገለጻ አድርገዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ቆላ ሻራ ቀበሌ እያስጠገነ ያለውን የባዮ-ጋዝ ማብለያ ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዙር ሳይት ምልከታ መጋቢት 14/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ማፍለቂያ ማዕከል ለጫሞና ለአርባ ምንጭ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች በሥራ ፈጠራ አመለካከትና የሥራ ፈጠራ ክሂሎት ላይ መጋቢት 10/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

አቶ ካሣሁን ደለለኝ ከአባታቸው ከአቶ ደለለኝ ታችበሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዓለምነሽ ተረፈ በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ክ/ሀገር በሳውላ ከተማ ነሐሴ 30/1976 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በግማሽ ዓመት ውስጥ የተከናወኑና በመከናወን ላይ የሚገኙ የምርምር ሥራዎችን አስመልክቶ መጋቢት 13/2014 ዓ/ም በኮሌጁ ግቢና በዩኒቨርሲቲው የእርሻ ምርምር ጣቢያ የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል፡፡