የዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ትምህርት ክፍል በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› የትምህርት ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ በ3ኛ ዲግሪ ለማስመረቅ የሚያስችለውን ቅድመ ሁኔታ አጠናቋል፡፡ ዕጩ ተመራቂ ሙላቱ ኦሴ ለምረቃ ብቁ የሚያደርገውን ጥናታዊ ጽሑፍ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን በተገኙበት ሰኔ 04/2013 ዓ/ም አቅርቧል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ በትምህርት ጥራትና አግባብነት ዙሪያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ፕሮፌሰሮች ካውንስልና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተፎካካሪ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ሰኔ 05/2013 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለጨንቻ ወረዳ ሆሎኦ ላካ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ሰኔ 3/2013 ዓ/ም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ከ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አኳያ - የትምህርት ፕሮግራም

ለሁሉም ትምህርት ክፍሎች፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ ተማሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አባላት በሙሉ

በ6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን በምርጫው መሳተፍ ይችሉ ዘንድ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠ አቅጣጫ ከሰኔ 7-21 ያለው ጊዜ የገጽ ለገጽ ትምህርት አይኖርም፡፡ ነገር ግን በቀጣይ የሚኖረን ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በBiology ትምህርት ክፍል የ3ኛ ዲግሪ ዕጩ ተመራቂ ሙላቱ ኦሴ በʻbiodiversity Conservation and Management የትምህርት ፕሮግራም ሲከታተል የቆየውን ትምህርት በማጠናቀቅ ለምርቃት ዝግጁ የሚያደርገውን በʻHabitat Fragmentation Effects on Vascular Epiphytes, Bryophytes and Predator-Pest Dynamics in Kafa Biosphere Reserve and Nearby Coffee Agro-ecosystem, South West Ethiopia በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን የመመረቂያ ጽሑፍ ከውጪና ከሀገር ውስጥ እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲው የተጋበዙ ምሁራን በተገኙበት ሰኔ 4/2013 ዓ/ም በዓባያ ካምፓስ ያቀርባል፡፡