በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ት/ክፍል በ ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ ግንቦት 13/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ  የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በአባያ ካምፓስ አዲሱ ማኔጅመንት ሕንፃ አዳራሽ ያቀርባል፡፡

ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ የመመረቂያ ምርምሩን ‹‹Plant Communities, Socioeconomic Values, and Carbon Stock Potential of Forest Patches in Wolaita, Southern Ethiopia ›› በሚል ርእስ አከናውኗል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የብዝኃ ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከል ተመራማሪዎች ከእምቦጭ አረም የተለያዩ ቁሳቁሶችን በመሥራት አረሙ በውኃ አካላት ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ማዕከል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ  ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከወረዳው ጤና ጣቢያዎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በአዲሱ የኤች አይ ቪ ምርመራ አልጎሪዝም /HIV Testing Algorithm/ እና በወባ በሽታ ሕክምናና ምርመራ አዳዲስ አሠራሮች /Malaria Technical Update/ ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ግንቦት 4/2016 ዓ/ም ተጠናቋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች የአመራርነት እና የአስተዳደር ክሂሎት ሥልጠና ሚያዝያ 22/2016 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ የ2015/16 የሥራ ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ ለ2017/18 ለሁለት ዓመት የሚያገለግሉ አዲስ ሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ከግንቦት 3/2016 ዓ/ም ጀምሮ እየተካሄደ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡