- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማኅብረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በምርምር ትብብር ፕሮጀክቶች ችግሮችና ዕድሎች ዙሪያ ሐምሌ 13/2016 ምክክር አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ የኢኮኖሚክስ ትምህርት መስክ 4ኛ ዓመት የሳምንት መጨረሻ ተማሪ የነበረው ተማሪ ዋና ሳጅን መለሰ አባይነህ ከቡልቂ ወደ አደጋው ቦታ ተጎጂዎችን ለመርዳት በሄደበት አደጋው በድጋሚ በመከሰቱ በድንገት ሕይወቱ ያለፈ በመሆኑ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዞመዶቹና ጓደኞቹ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው በተለይ ለሳውላ ካምፓስ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።
- Details
አቶ ነጋልኝ ስለሺ ከአባታቸው ከአቶ ስለሺ ስሜ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብሩክነሽ ብርሃኑ ሚያዝያ 08/1987 ዓ.ም በገዜ ጎፋ ወረዳ ቡልቂ ከተማ ተወለዱ፡፡
- Details
በፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለተባባሪ አሠልጣኝነት በወጣው ማስታወቂያ መሠረት በተወሰነው ጊዜ በኮሚሽኑ ኢ-ሜይል መረጃችሁን የላካችሁ አመልካቾች የላካችሁትን መረጃ ኮፒ /Hard Copy/ እስከ 18/11/2016 ዓ.ም ድረስ በዋናው ግቢ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ቢሮ እንድታቃርቡ እንገልጻለን፡፡
Read more: በፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለተባባሪ አሠልጣኝነት በወጣው ማስታወቂያ ላመለከታችሁ በሙሉ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ትናንት ረፋድ አካባቢ በተከሰተው የመሬት ናዳ አደጋ ምክንያት በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ስም እየገለጸ ለኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ፣ ለዞኑና ለክልሉ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።