በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች እድሳት የተደረገላቸው የ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች ማደሪያ ሕንፃዎችና በግቢ ውበት የተሠሩ ሥራዎች ተጠናቀው ከመጋቢት 8/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአገልግሎት እንዲበቁ ተደርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ት/ቤቶች የ2014 የትምህርት ዘመን 1ኛ ሴሚስተር አፈፃፀም ውይይትና የወላጅ በዓል የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት መጋቢት 10/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግዢና ንብረት አስተዳደር እና የፋይናንስና በጀት አስተዳደር ባለሙያዎች እንዲሁም ለማኔጂንግ ዳይሬክተሮች በግዢ ዕቅድ፣ በግዢ መርሆዎች፣ በግዢ አፈፃፀም አቤቱታ አቀራረብ፣ በጨረታ ሰነድ ዝግጅትና የውል አስተዳደር እና በንብረት አስተዳደር ዕርሰ ጉዳዮች ላይ ከመጋቢት 08-09/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በክላስተሩ የሚገኙ ቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማት ቀጠናዊ ትስስር ፎረም በዳሰሳ ጥናት የተገኙ ውጤቶች፣ የፎረሙ የ2013 ዓ/ም አፈፃፀም ክለሳና የ2014 ዓ/ም ዕቅድ ላይ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የካቲት 26/2014 ዓ.ም በጊዶሌ ከተማ ውይይት አካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከደራሼ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በወረዳው ለሚገኙ እንዲሁም ከቡርጂና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 22 የፕላን መምሪያ እና የግብርናና ገጠር ልማት ሠራተኞች ከመጋቢት 8-10/2014 ዓ/ም ለሦስት ቀናት በGIS ሶፍትዌር ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ