ከ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አኳያ - የትምህርት ፕሮግራም

ለሁሉም ትምህርት ክፍሎች፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ ተማሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አባላት በሙሉ

በ6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን በምርጫው መሳተፍ ይችሉ ዘንድ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠ አቅጣጫ ከሰኔ 7-21 ያለው ጊዜ የገጽ ለገጽ ትምህርት አይኖርም፡፡ ነገር ግን በቀጣይ የሚኖረን ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡፡

  1. የ2012 1ኛ ዓመት የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች የትምህርት ፕሮግራም ምደባችሁ መሠረት ከወዲሁ አስፈላጊውን ጨርሳችሁ ወደ ካምፓሶቻችሁ (የጤና፣ የግብርና እና የማኅበራዊና ስነ-ሰብ ሳይንስ ተማሪዎች) እንድትሄዱና በ22/10/2013 በየተመደባችሁበት ትምህርት ክፍል ትምህርት ይጀመራል፡፡
  2. ሌሎች መደበኛ ተማሪዎች የ2013 1ኛ መንፈቅ የክፍል ትምህርት በ05/10/2013 የሚጠናቀቅ ሲሆን ማጠቃለያ ፈተና ከ22/10/2013 ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
  3. የ2013 አዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ ቀን ከ21/10/2013 በኋላ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
  4. ምርጫ ለመምረጥ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ከሰኔ 8 ቀን እስከ 20 ቀን 2013 ዓ.ም ትምህርት የማይኖር ሲሆን በዚሁ ጊዜ ተማሪዎች ወደመጡባቸው አካባቢዎች በመሄድ ምርጫ ላይ ይሳተፋሉ::
  5. ትምህርት ዝግ በሆነበት ቀናት በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ መቆየት የሚፈልጉ መደበኛ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲውን ሕግና ደንቦችን በማክበር መቆየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
  6. ሌሎች ኢ-መደበኛ ትምህርቶች የተከታታይ (Extenstion) እና ሳምንት መጨረሻ (Weekend) ተማሪዎች ከምርጫው በኋላ በሚኖረው አንድ ሳምንት (ከሰኔ 15 እስከ 20/2013 ዓ.ም ብቻ) የመማር ማስተማር ሂደት አይኖርም፡፡
  7. ሁሉም የድህረ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ ከምርጫው በኋላ በሚኖረው አንድ ሳምንት (ከሰኔ 15 እስከ 20/2013 ዓ.ም ብቻ) ብቻ ትምህርት በገጽ ለገጽ ምትክ በኦንላይን (Virtual) አማራጭ ይካሄዳል፡:


በመሆኑም የሚመለከታችሁ የዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ማኅበረሰቡ በሙሉ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት አስፈላጊውን ዝግጅትና ክትትል በማድረግ እንዲፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዪኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት