የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በክላስተሩ የሚገኙ ቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማት ቀጠናዊ ትስስር ፎረም በዳሰሳ ጥናት የተገኙ ውጤቶች፣ የፎረሙ የ2013 ዓ/ም አፈፃፀም ክለሳና የ2014 ዓ/ም ዕቅድ ላይ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የካቲት 26/2014 ዓ.ም በጊዶሌ ከተማ ውይይት አካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከደራሼ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በወረዳው ለሚገኙ እንዲሁም ከቡርጂና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 22 የፕላን መምሪያ እና የግብርናና ገጠር ልማት ሠራተኞች ከመጋቢት 8-10/2014 ዓ/ም ለሦስት ቀናት በGIS ሶፍትዌር ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሰቲ የምር/ማኅ/አገ/ም/ፕ/ጽ/ቤት ከ‹‹አገልግል የተፈጥሮ ልማትና ጥበቃ የበጎ አድራጎት ማኅበር›› ጋር በመተባበር ‹‹ወጣትነት፣ ህልምና ሀገራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ከመጋቢት 5-6/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

 የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ግብርና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር ከማዕከሉ ለተወጣጡ የምርምር ባለሙያዎች ከየካቲት 30 - መጋቢት 03/2014 ዓ/ም የሚትዎሮሎጂ መረጃ ትንተናና ቪዢዋላይዜሽን (Meteorological Data Analysis & Visualization) ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከ12 ሆስፒታሎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎችና ሐኪሞች በ ‹‹Clinical Preceptorship›› ዙሪያ ከመጋቢት 5-7/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ