‹‹የዜጎች ቀጥተኛ ሚና ለሁለንተናዊ ብልጽግና›› በሚል መሪ ቃል የምሁራን የውይይት መድረክ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምር ዳይሬክቶሬት ከማኅበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ፣ ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እንዲሁም ከስነ ትምህርትና ስነ ባህርይ ሳይንስ እና ከሕግ ት/ቤት ጋር በመተባበር 8ኛውን ሀገር አቀፍ ምርምር ለልማት አውደ ጥናት ከግንቦት 05-06/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ 

AMU-IUC ፕሮግራም ለሁለተኛ ዙር ላወጣው የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል አመልካች ሴት መምህራን ግንቦት 4/2014 ዓ/ም የማነቃቂያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለዓባያ፣ ጫሞና ነጭ ሳር ካምፓስ የአስተዳደር ሠራተኞች የጾታና የሥርዓተ ጾታ ምንነት፣ የጾታዊ ጥቃቶች ምንነትና ዓይነቶች፣ ጾታዊ ጥቃቶችን መከላከያ መንገዶች እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 02-03/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የእግር ኳስ ክሂሎት ላላቸው በአርባ ምንጭ አካባቢ ከሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትና ትምህርት ቤቶች ለተመለመሉ ከ17 ዓመት በታች ለሆኑ 60 ታዳጊዎች ሚያዝያ 28/2014 ዓ/ም የተለያዩ የእግር ኳስ ቁሳቁሶችን አበርክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ