በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለሕክምና ት/ቤት መመህራንና ተማሪዎች አገልግሎት የሚውል “UpToDate” የተሰኘ ሶፍትዌርን ለ5 ዓመታት በነፃ የመጠቀም ፈቃድ ማግኘቱ ተገለፀ፡፡

‹‹Open Forum on Agricultural Bio-technology›› በሚል ርዕስ ‹OFAB-Ethiopia› የደቡብ ምዕራብ ቅርንጫፍ ያዘጋጀው ፎረም ሚያዝያ 08/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር /INSA/ ጋር በመተባበር በድሮን ካሜራ አጠቃቀም ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የትምህርትና ሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ከነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክና ከ“GIZ” ለተወጣጡ ባለሙያዎች ከሚያዝያ 3-12/2014 ዓ/ም ድረስ ለ10 ቀናት የቆየ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ 

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የሕንድ አምባሳደር ሺሪ ሮበርት ሼትኪንቶንግ (Shri Robert Shetkintong) በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ከሚያስተምሩ ሕንዳውያን መምህራን ጋር ሕንድ ሀገር ከሚገኙ ተቋማት ጋር በትብብር ግንኙነት በመፍጠር ምርምር፣ ማኅበረሰብ አገልግሎትና የቴክሎጂና የፈጠራ ሥራዎችን በጋራ መሥራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ሚያዝያ 12/2014 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል በኢንፎማይንድ ሶሉሽንስ ንዑስ የቢዝነስ ዩኒት ከሆነው ደረጃ ዶት ኮም ኃ.የተ.የግ. ድርጅት /Dereja.Com/ ጋር በመተባበር በተለያዩ የትምህርት መስኮች በ2014 ዓ/ም ለሚመረቁ ተማሪዎች ከሚያዝያ 4-7/2014 ዓ/ም የተቀጣሪነት ክሂሎት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡