Arba Minch University and the Christian Aid team visited Dingamo Pico-hydropower project which is under construction at Gamo Zone, Kamba Zuria Woreda with budget from Arba Minch University and Christian Aid, on June 13, 2023. Click here to see the pictures.

‹‹Brighter Generation›› የተሰኘ ድርጅት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹STEM›› ማዕከል ጋር በመተባበር በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተወጣጡ የተሻለ የመግባባት ችሎታና የትምህርት ውጤት ያላቸው የ9ኛና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ10 ሳምንታት የሚቆይ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ተግባቦትና የአመራር ክሂሎት የበይነ-መረብ ሥልጠና ለመስጠት ሰኔ 17/2015 ዓ/ም የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል አዘጋጅነት በሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች መካከል ሲደረግ የቆየው የ2015 ዓ/ም 2ኛ ዙር የንግድ ሥራ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ሰኔ 16/ 2015 ዓ/ም ተጠናቋል፡፡ በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ስድስት የቢዝነስ ፈጠራ ሃሳቦች ቀርበው ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ተወዳዳሪዎች የማበረታቻ ገንዘብ ሽልማት እንዲሁም ለቀሪዎቹ ተወዳዳሪዎች የምስክር ወረቀት ተበርክቷል፡፡ የተሻሻለ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን፣ ዘመናዊ ጡብ ማምረቻ፣ ከአፈር ውጭ ውሃን በመጠቀም የጓሮ አትክልቶችን ማምረትና ከሙዝ ግንድ ወረቀት ማምረት ከቀረቡ የፈጠራ ሥራ ሃሳቦች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ከጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን  ቴክኖሎጂ መምሪያ ጋር በመተባበር ከዞኑ  14 ወረዳዎች፣ ስድስት የከተማ አስተዳደሮችና አምስት የግል ማኅበራት ለተወጣጡ የICT እና የቢሮ ማሽን ጥገና ባለሙያዎች ከሰኔ 12- 16/2015 ዓ/ም የቢሮ ማሽን ጥገና ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎክን የመጻሕፍትና መረጃ ማዕከል ከበጎ አድራጎት ማዕከል ጋር በመተባበር  በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ልማት እና አርባ ምንጭ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ ለማረሚያ ብሩህ ተስፋ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ለሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ከተለያዩ አካላት በልገሳ ያገኟቸውን የመማሪያ ማጣቀሻ መጻሕፍት እና አልባሳት ድጋፍ ግንቦት 22/2015 ዓ/ም  አበርክተዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡