Solve IT 2023 registrations are now OPEN! Don't miss your opportunity to be part of the most exciting innovation competition in Ethiopia.

በዓለም ለ19ኛ በሀገራችን ለ11ኛ ጊዜ የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን የመከላከልና መቆጣጠር ቀን/Antimicrobial Resistance Day/ "የአመራር ሚና የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከልና መቆጣጠር" በሚል መሪ ቃል ከኢትዮጵያ ፋርማሲዎች ማኅበር፣ ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፋርማሲ ት/ክፍልና ከኢትዮጵያ ፋርማሲ ተማሪዎች ማኅበር ጋር በመተባበር ሰኔ 12/2015 ዓ.ም ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአባልነት የተካተተበት እንሰትን ብሔራዊ ስትራቴጂክ ሰብል ለማድረግ የተቋቋመው የእንሰት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ከሚቴ አባላት ዩኒቨርሲቲው በመስኩ እያከናወናቸው የሚገኙ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማኅበረሰብ ጉድኝት ሥራዎችን በምርምር ቤተ-ሙከራዎችና ሠርቶ ማሳያዎች ላይ በመገኘት ከሰኔ 11-12/2015 ዓ/ም ምልከታና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ/Justice for All Prison Fellowship Ethiopia/ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በወንጀል ምርመራና ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃት ላይ ለደቡብ ክልል መርማሪ ፖሊሶች ከሰኔ 9-10/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ጋር በመተባበር ለኮሌጁ መምራን “Grant Proposal Writing and Manuscript Preparation Skills” በሚል ርዕስ ከሰኔ 8-9/2015 ዓ/ም የክሂሎት ማሻሻያ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡  በዕለቱም ከአሶሴሽኑ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ