- Details
Solve IT 2023 registrations are now OPEN! Don't miss your opportunity to be part of the most exciting innovation competition in Ethiopia.
- Details
በዓለም ለ19ኛ በሀገራችን ለ11ኛ ጊዜ የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን የመከላከልና መቆጣጠር ቀን/Antimicrobial Resistance Day/ "የአመራር ሚና የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከልና መቆጣጠር" በሚል መሪ ቃል ከኢትዮጵያ ፋርማሲዎች ማኅበር፣ ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፋርማሲ ት/ክፍልና ከኢትዮጵያ ፋርማሲ ተማሪዎች ማኅበር ጋር በመተባበር ሰኔ 12/2015 ዓ.ም ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 11ኛው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን የመከላከልና መቆጣጠር ቀን ተከበረ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአባልነት የተካተተበት እንሰትን ብሔራዊ ስትራቴጂክ ሰብል ለማድረግ የተቋቋመው የእንሰት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ከሚቴ አባላት ዩኒቨርሲቲው በመስኩ እያከናወናቸው የሚገኙ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማኅበረሰብ ጉድኝት ሥራዎችን በምርምር ቤተ-ሙከራዎችና ሠርቶ ማሳያዎች ላይ በመገኘት ከሰኔ 11-12/2015 ዓ/ም ምልከታና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ የእንሰት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ኮሚቴ ውስጥ አባል ሆኖ እየሠራ ነው
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ/Justice for All Prison Fellowship Ethiopia/ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በወንጀል ምርመራና ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃት ላይ ለደቡብ ክልል መርማሪ ፖሊሶች ከሰኔ 9-10/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በወንጀል ምርመራና ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃት ላይ ለደቡብ ክልል መርማሪ ፖሊሶች ሥልጠና ተሰጠ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ጋር በመተባበር ለኮሌጁ መምራን “Grant Proposal Writing and Manuscript Preparation Skills” በሚል ርዕስ ከሰኔ 8-9/2015 ዓ/ም የክሂሎት ማሻሻያ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ በዕለቱም ከአሶሴሽኑ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ድጋፍ በሚያስገኙ ፕሮጀክቶች አዘገጃጀትና በምርምር ጽሑፍ ኅትመት ላይ የክሂሎት ማሻሻያ ሥልጠና ተሰጠ