በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ አዘጋጅነት ከጥር 25/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የዋናው ግቢ ተማሪዎች የእርስ በእርስ እግር ኳስ ውድድር እየተካሄደ ነው፡፡ ውድድሩ በሁለት ምድብ በስድስት ቡድኖች መካከል የሚከናወን ሲሆን በ2016 ዓ/ም ለሚካሄደው የካምፓሶች ውድድር ዋናውን ግቢ የሚወክሉ ተጫዋቾችን ለመለየት ያለመ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ‹‹Development Economics›› ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ሰሎሞን ከበደ የካቲት 01/2016 ዓ/ም የምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

መቀመጫውን ስዊድን ሀገር ያደረገው ሂዩማን ብሪጅ /HUMAN BRiDGE የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታልን የካቲት 01/2016 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ የኒቨርሲቲ የፀረ ሙስናና ሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለጫሞ፣ ዓባያና ሳውላ ካምፓሶች አዲስ ገቢ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዲስፕሊን መመሪያ ላይ ከጥር 25 - የካቲት 02/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ10 ደቂቃ አንድ ኩንታል በቆሎ መፈልፈል የሚችል ማሽን ሠርቶ የካቲት 02/2016 ዓ/ም በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሀኒቃ ቀበሌ ሶቦ መንደር ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለሙከራ አቅርቧል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ