- Details
አርበ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ጋር በመተባበር ‹‹አርባ ምንጭ ታንብብ›› በሚል መሪ ቃል ከጥር 18-21/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ከተማ የንባብ ሳምንት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ‹‹አርባ ምንጭ ታንብብ›› በሚል መሪ ቃል የንባብ ሳምንት በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሄደ
- Details
የዩኒቨርሲቲው የሥራ ፈጠራ ልማት እና ማበልጸጊያ ማዕከል ከኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት/ Entrepreneurship Development Institute (EDI) ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር ከጥር 13-18/2016 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራን የኢንተርፕርነርሽፕ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በኢንተርፕርነርሽፕ ምንነት፣ የቢዝነስ ፕላን አዘገጃጀት፣ የስኬታማ ኢንተርፕርነሮች ባህርያት እና መሰል ርእሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ጥር 17/2016 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ተገመገመ
- Details
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ከ10 ዩኒቨርሲቲዎች ለተወጣጡ የሥነ ልቦና ባለሙያዎች እና የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክተሮችና አስተባባሪዎች በተማሪ ልማት ዙሪያ ከጥር 16-17/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለሥነ ልቦና ባለሙያዎችና የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች በተማሪ ልማት ዙሪያ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት/FDRE Construction Management Institute/ ጋር በመተባባር “Building Information Management/BIM”በሚል ርዕስ ለዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ እና ለውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች መምህራን፣ ለዩኒቨርሲቲው ግንባታ ፕሮጀክትና ለፋሲሊቲ አስተዳደር ዘርፍ ባለሙያዎች ከጥር 13 - 30/2016 ዓ.ም ድረስ ስለግንባታ ሞዴልንግ ቴክኖሎጂ ሥልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂና ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች መምህራን ስለግንባታ ሞዴልንግ ቴክኖሎጂ ሥልጠና እየተሰጠ ነው