‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት›› መርሃ-ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ መስከረም 21/2014 ዓ/ም በማዕከል ደረጃ ተካሂዷል፡፡ በቀጣይ ቀናት መርሃ-ግብሩ በዩኒቨርሲቲው ሁሉም ካምፓሶች እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ  

ለ1 ወር በተለያዩ ጤና ጣቢያዎች በቡድን ሥልጠና ፕሮግራም/Team Training Program/TTP/ ላይ የቆዩ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች የመጨረሻ ሪፖርታቸውን ገምገሚ መምህራን በተገኙበት ከመስከረም 14-15/2014 ዓ/ም መስክ በወጡባቸው ጤና ጣቢያዎች አቅርበዋል፡፡ ቆላ ሼሌ፣ ኮንሶ ካራት፣ አረካ፣ ቦዲቲና ብርብር ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች ተማሪዎቹ በሥራ የቆዩባቸው የጤና ተቋማት ናቸው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ    

በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገነባው የአረጋውያንና ሕፃናት ማዕከል ገቢ ማሰባሰቢያ ‹‹ኑ የነገ ቤታችንን እንሥራ›› በሚል መሪ ቃል መስከረም 11/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ከተማ የማነቃቂያ የእግር ጉዞ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ረ/ፕ አባይነህ ኡናሾ ከአባታቸው ከአቶ ኡናሾ ጋንዲሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ፋስቴ ጡኖ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ ጠቅላይ ግዛት ጋርዱላ አውራጃ ዘይሴ አካባቢ በ1950 ዓ/ም ተወለዱ፡፡