የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በጋሞ፣ ጎፋ፣ ኮንሶና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ጥቅምት 20/2014 ዓ/ም ክላስተራዊ የውይይት ፎረም አካሂዷል፡፡ 

መ/ር መቆያ መርጊያ ከአባታቸው ከአቶ መርጊያ በላይነህ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አባይነሽ አራጫ በጋሞ ዞን ቦንኬ ወረዳ ገረሴ ከተማ ግንቦት 14/1983 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ በርቀት ትምህርት መርሃ-ግብር በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የተቀመጠውን የመግቢያ መስፈርት የሚያሟሉ አመልካቾችን በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ፣ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ፣ በታሪክና ቅርስ አስተዳደር፣ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ - አማርኛ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ፣ በሥነ-ዜጋና ሥነ-ምግባር ጥናት፣ በሶሾሎጂና ሶሻል አንትርፖሎጂ እና በፒጂዲቲ ትምህርቶች በአርባ ምንጭ፣ በአዲስ አበባ፣ በሳውላ፣ በምዕራብ ዓባያ፣ በካምባ፣ በቁጫ፣ በኮንሶ፣ በባስኬቶ እና በአማሮ ኬሌ ልዩ ወረዳዎች ማዕከላትን ከፍቶ በመጀመሪያ ዲግሪ ማሠልጠን ይፈልጋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ነባር ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ ጥቅምት 23-24/2014 ዓ/ም የሚካሄድ ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው ጥቅምት 29/2014 ዓ/ም ይሆናል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና “Christian Aid” የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት የተሠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንሰት አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለማዳረስ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ ከድርጅቱ የመጡ የሥራ ኃላፊዎች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በመሆን ጥቅምት 9/2014 ዓ/ም በዶርዜና ግርጫ ምርምር ማዕከላት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በቅርቡም የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር እንደሚገባ ታውቋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ