አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው የ34 ዓመታት ታሪክ የመጀመሪያውን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ በግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የእንስሳት ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ለሆኑት ለዶ/ር ይስሃቅ ከቸሮ ከበደ ሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን በድኅረ ምረቃ 7 እና በቅድመ ምረቃ 674 በአጠቃላይ 681 ተማሪዎች መስከረም 30/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 252ቱ ሴቶች ናቸው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ      

በዩኒቨርሲቲው 6ኛው ዙር ዓመታዊ የማኅበረሰብ ሳምንት ‹‹በተፈጠረው እድል ማኅበረሰባችንን እናገልግል›› በሚል መሪ ቃል መስከረም 28/2014 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥራ ፈጠራ ልማት ማፍለቂያ ማዕከል በሁሉም ካምፓሶች ለሚገኙ የ2014 ዓ/ም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ከመስከረም 25-26/2014 ዓ/ም የሥራ ፈጠራ ክሂሎት /Entrepreneurship Skill/ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማት ማፍለቂያ ማዕከል የቢዝነስ ሃሳብ አቅርበው ማጣሪያውን ላለፉ 5 የ2014 ዓ/ም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መስከረም 26/2014 ዓ/ም ሽልማት አበረከተ፡፡