The 2nd International Conference on Omotic Language Studies

The 2nd International Conference on Omotic Language Studies will be held in Arba Minch University, Ethiopia, on September 20-22, 2021. The conference is aimed at bringing together scholars, linguists, researchers, language activists and others working on Omotic linguistics from around the world. The majority of the Omotic languages have been largely oral and have not been described and developed for modern use such as for education, media, literature, and the like. We believe that such kind of international conferences will serve as a forum for exchanging views on recent research endeavors and contributes to the quality of the scientific study and development of these languages.

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ‹‹የምሁራንና የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ እውን መሆን!›› በሚል መሪ ቃል ግንቦት 24/2013 ዓ.ም ሀገራዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለአርባ ምንጭ ከተማ ማኅበራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በተለያዩ የሕግ ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 18-19/2013 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከምዕራብ ዓባያና ከአርባ ምንጭ ከተማ ለተወጣጡ የ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራን ግንቦት 14/2013 ዓ/ም የተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ንባብ ክሂሎት ማሻሻያ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፊደላት፣ ድምጽና ስያሜያቸው እንዲሁም ተነባቢና አናባቢ ድምጾች በቃላት ውስጥ ሲገቡ የሚያመጡትን ለውጥ ለተማሪዎቹ የሚያስተምሩበት ስነ-ዘዴ በስፋት ተዳሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ኢንስቲትዩት ከኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 5ኛው ‹‹ሀገረሰባዊ ዕውቀት ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት›› ሀገራዊ ዓውደ ጥናት ግንቦት 26/2013 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ተካሂዷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ