የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ ተመራማሪዎችና የአስተዳደር ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ድጋፍ ለማድረግ ነሐሴ 8/2013 ዓ/ም በዋናው ግቢ ባካሄዱት ውይይት የ 1 ወር ደመወዛቸው በበጀት ዓመቱ ተቆራጭ ተደርጎ ድጋፍ እንዲደረግ ወስነዋል፡፡ ከገንዘብ ድጋፉ በተጨማሪ ፈቃደኛ ተሳታፊዎች የደም ልገሳ አከናውነዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ AMU-IUC ፕሮግራም ከGHENT ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አጥቢ እናቶች ከ6 ወር በታች የሆኑ ሕፃናትን የእናት ጡት ወተት ብቻ ማጥባታቸውን ለመለየት የሚያገለግል የምርምር መለኪያ ዘዴ ላይ ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ለተወጣጡ 40 መምህራን ነሐሴ 7/2013 ዓ/ም የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ነሐሴ 4/2013 ዓ/ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ለ 3 መምህራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጠ ሲሆን በሌሎች የተለያዩ ጉዳዩችም ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ከኮሌጁ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ ከጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት ት/ክፍል እንዲሁም ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት (GIZ) ጋር በመተባበር ከጋሞ ዞን ወረዳዎች ለተወጣጡ የተፈጥሮ ሀብትና ደን ልማት ባለሙያዎች በ‹‹Geographic Information System(GIS) እና ‹‹Global Positioning System››(GPS) ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከሐምሌ 26 - ነሐሴ 1/2013 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በዩኒቨርሲቲው የሕግ ትምህርት ቤት ለሚማሩ 59 የ5ኛ ዓመት የሕግ ተመራቂ ተማሪዎች እንዲሁም ከዚህ ቀደም በተለያዩ ቦታዎች የሕግ ትምህርታቸውን ተከታትለው የመውጫ ፈተናውን ላላለፉ 87 ተማሪዎች ከሐምሌ 27-30/2013 ዓ/ም የ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ