Ministry of Science and Higher Education’s maiden event - Higher Education, Research, Technology & Industry Linkage - HEART Convention–2021, has done more than what it expected. Its acknowledgement and felicitation of crème de la crème from academic and research fields has literally set the ball rolling as those feted in different categories having got much-needed fillip vowed to raise the bar in their endeavors.

ʻʻኢትዮጵያን እናልብሳት!ʼʼ በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 20/2013 ዓ/ም ከጧቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው በአንድ ቀን 100 ሺህ ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን ዕቅድ ከከተማውና አካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ለማሳካት በቤሬ ተፋሰስ እንዲሁም የፊታችን ዓርብ ሐምሌ 23/2013 ዓ/ም ʻʻGreen Legacy, Green Campus!” በሚል መሪ ቃል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሁሉም የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች 3ኛው አገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ይካሄዳል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ በቅርቡ በሞት ለተለዩት መ/ር ወርቁ ውበት የተሰማውን ሐዘን ለመግለጽ ሐምሌ 16/2013 ዓ.ም የሻማ ማብራት ፕሮግራም አካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ በአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት፣ በኮሌጁ ዲን፣ በመምህራንና በተማሪዎች በንግግር፣ በጽሑፍና በግጥም የሐዘን መግለጫ ቀርቧል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 114 ሺህ ብር የሚያወጡ የሕክምና ቁሳቁሶችን ለሰላም በር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሐምሌ 14/2013 ዓ/ም ድጋፍ አድርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ሀገራችን ኢትዮጵያ በመንግሥትና በሕዝብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እየገነባች የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ መላው የዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብና ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!!

ግድቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለሀገራችን ዕድገት መፋጠን በሙሉ አቅም አገልግሎት መስጠት እስኪጀምር ለግንባታው የነበረው ሁለንተናዊ ሕዝባዊ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ማኅበረሰቡም እንደ ከዚህ ቀደም ሁሉ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቀሪ የግንባታ ሥራዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ አስተዋፅዖ ማድረጋቸውን አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጣለሁ።