የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሐምሌ 18/2014 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዓሣን የፕሮቲን ይዘት ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ከሚሠራው ‹‹ዓሢቱ›› ከተሰኘ ድርጅት ጋር ዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሐምሌ 18/2014 ዓ/ም ተፈራርሟል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የውሃ አቅርቦትና አካባቢ ምኅንድስና ት/ክፍልና በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ት/ክፍል አስተባባሪነት ከሐምሌ 11-15/2014 ዓ/ም ለ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች የ ‹‹Python Programing Language›› ሶፍትዌር ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ትምህርትና የሥነ-ባህርይ ሳይንስ ት/ቤት በከፍተኛ ዲፕሎማ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን 150 ወንድ እና 48 ሴት በድምሩ 198 ሠልጣኝ መምህራን ሐምሌ 16/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ