የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች በካምባ፣ ገረሴ፣ ቆላ ሼሌ፣ ብርብር፣ ዋጂፎ፣ ቦዲቲና አረካ ጤና ጣቢያዎች በቡድን ሥልጠና ፕሮግራም የቆዩበትን የመስክ ሪፖርት የኮሌጁ ገምጋሚ መምህራን በተገኙበት ነሐሴ 16/2014 ዓ/ም አቅርበዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በዩኒቨርሲቲው የሥልጣን ዘመናቸውን ያጠናቀቁትን የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር የሚተኩ አመራሮችን አወዳድሮ ለመመደብ የእጩ መልማይና የምልመላ ኮሚቴ አባላት
ነሐሴ 16/2014 ዓ/ም ተመርጠዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛ መርሃ-ግብር ለተመረቁ ተማሪዎች ወንድ 3.5 እና ከዚያ በላይ፣ ሴት 3.25 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ በ2015 የትምህርት ዘመን ነፃ የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል ለ18 ተማሪዎች (AMIT 2፣ AWTI 2፣ CBE 2, CSSH 2, CMHS 2, CAS 2, CNS 2, School of Law 1, school of PBS 1, Sawula campus 2)  አወዳደሮ ለመስጠት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚትፈልጉ የ2014 ተመራቂ ተማሪዎች ( መስከረም 29/30 እና ሰኔ 25/26 2014 ዓ.ም የተመረቃችሁ) ከነሐሴ 18-27/2014 ዓ/ም ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት እንድትመዘገቡ እየገለጽን፡-

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ/ICT/ ዳይሬክቶሬት ከኮምፒውቲንግና ሶፍትዌር እና ከኤሌክትሪካልና ኮሚፒውተር ምኅንድስና ፋከልቲዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የዲጂታል ሊትረሲ የሥልጠናና ሰርተፊኬሽን ወርክሾፕ ከነሐሴ 11-14/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ ለአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ከዩኒቨርሲቲው መምህራን መካከል አወዳድሮ ለመመደብ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም የአመልካቾች ትምህርት ደረጃ 2ኛ ዲግሪ (ማስትሬት) ከረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ጋር እና ከዚያ በላይ ሆኖ ከማመልከቻቸው ጋር ቀጥሎ የተዘረዘሩ ማስረጃዎችን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡