የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ ዩኒቨርሲቲውን በሚቀጥሉት 6 ዓመታት በፕሬዝደንትነት የሚመራውን ኃላፊ ማወዳደር ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም የአመልካቾች ትምህርት ደረጃ ሁለተኛ ዲግሪ (ማስትሬት) ከረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ጋር እና ከዚያ በላይ ሆኖ ከማመልከቻቸው ጋር ቀጥሎ የተዘረዘሩ ማስረጃዎችን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹አሻራችን ለትውልዳችን›› እና ‹‹Green Legacy; Green Campus!›› በሚሉ መሪ ቃሎች በቤሬ ተፋሰስ ችግኝ በመትከል ነሐሴ 12/2014 ዓ/ም 4ኛውን ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በይፋ አስጀምሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ለሳውላ፣ ጨንቻ፣ ጫኖ ዶርጋ፣ ጻይቴና ጋርዳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች እና በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ወጣት ማዕከላት በተለያዩ የትምህርት አይነቶች የተዘጋጁ የማጣቀሻና ልብ ወለድ መጻሕፍትን ሐምሌ 10/2014 ዓ/ም አበርክቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ ላይ ለመተግበር የታሰበውን የአነስተኛ መሬትና የውሃ አያያዝ ሥራዎች ፕሮጀክት በተመለከተ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች፣ ከኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን እና ከጋሞ ዞን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ነሐሴ 5/2014 ዓ/ም ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና አስተዳደር የ2ኛ ዲግሪ (MSc in Biodiversity Conservation and Management) እና በአካባቢያዊ ሳይንስ የ3ኛ ዲግሪ (PhD in Environmental Science)የትምህርት መርሃ ግብሮች ነሐሴ 9/2014 ዓ/ም የሥርዓተ ትምህርት የውጭ ግምገማ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ