የስብእና ግንባታ አነቃቂና የቢዝነስ ሥራዎች አማካሪ ወጣት ማንያዘዋል እሸቱ ‹‹ራስን ማወቅ፤ ለዓላማ መኖር›› በሚል መሪ ቃል ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዋናው ግቢና በጫሞ ካምፓስ በስብዕና ግንባታ ዙሪያ የካቲት 10/2014 ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሂሳብ ት/ክፍል ላለፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት እጩ ዶ/ር መኮንን ሬዲ የካቲት 11/2014 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት የምርምር ሥራቸውን አቅርበዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የስነ-ትምህርትና ስነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ለ2014 ዓ/ም አዲስ ተቀጣሪ መምህራን ከየካቲት 7-11/2014 ዓ/ም መሠረታዊ የማስተማር ሥነ-ዘዴ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ሥልጠናው የትምህርት ዕቅድ አዘገጃጀት፣ የክፍል ውስጥ የእንግሊዝኛ ቋንቋ አጠቃቀም፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሥነ-ምግባር ሕጎች፣ የክፍል አያያዝና ቁጥጥር፣ የትምህርት ምዘናና ተማሪ ተኮር የማስተማሪያ ሥነ-ዘዴ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ