- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚገኙ ት/ቤቶች ለተወጣጡ 100 የ7ኛና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ዓባያ ካምፓስና ዋናው ግቢ በሚገኙ ቤተ-ሙከራዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስናና ሒሳብ ትምህርት መስኮች ከጥር 28/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት የሚቆይ የተግባር ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡
- Details
በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮና በክልሉ በሚገኙ 7 ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በጋራ በተከናወኑ የፍትሕና የሕግ አገልግሎት ሥራዎች አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅናና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በፍትሕና የሕግ አገልግሎት ሥራዎች የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእውቅናና የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንግሊዝኛ ቋንቋና ስነ-ጽሑፍ ት/ክፍል ላላፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት እጩ ዶ/ር ማንጉዳይ መርጮ የካቲት 5/2014 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት የምርምር ሥራቸውን አቅርበዋል፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲው ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከ6ቱ ካምፓሶች የተለያዩ ሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ አስተባባሪዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ከየካቲት 01-02/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው የአእምሮ ዕውቀት፣ የስሜት ልህቀት፣ ስብእናና ተፈጥሯዊ ባህሪያት በስፋት ተዳሰዋል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት ት/ክፍል የ2ኛ ዓመት ተማሪ የነበረችው ጽጌረዳ ግርማይ በቅርብ ጓደኛዋ ተማሪ በደረሰባት የስለት ጥቃት ጥር 23/2014 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን አስመልክቶ በኮሌጁ አስተባባሪነት የካቲት 01/2014 ዓ/ም የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡
Read more: የተማሪ ጽጌረዳ ግርማይን ኅልፈተ ሕይወት አስመልክቶ የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ