የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማዕከል የዩኒቨርሲቲያችንን ማኅበረሰብ የሀገራችን ብሔራዊ ጉዳዮችን በሚያገኙት ሚዲያ ሁሉ (በዋነኛነት በሶሻል ሚዲያ ላይ) እንዲያስተጋቡና እንዲያስተዋውቁ ማስተባበር ዋና ተግባሩ ነው፡፡ ለዚህም ተግባር ይረዳ ዘንድ የሀገራችንን ብሔራዊ አጀንዳዎች ለዜጎች በስፋት ማስተዋወቅና ግንዛቤ ማስጨበጥ በጣም አስፈላጊና ቀዳሚ ሥራ ነው፡፡

ዓለም አቀፍ የነጭ ሪባን ቀን ‹‹በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ የኃይል ጥቃቶችን በመከላከልና በማስቆም አጋርነታችንን እናሳይ!›› በሚል መሪ ቃል ሳውላ ካምፓስን ጨምሮ በዩኒቨርሲቲው ሁሉም ካምፓሶች ከኅዳር 16/2014 ዓ/ም ጀምሮ ተከብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ከዛሬ ኅዳር 27/2014 ዓ/ም ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ ትምህርት እንድትጀምሩ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡

የሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለሚያስተምሩ ነባር የሕክምና መምህራን ‹‹Case Based Discussion›› በተሰኘ የሕክምና ትምህርት ማስተማሪያና የምዘና ዘዴ ላይ ከኅዳር 27 - ታኅሳስ 1/2014 ዓ/ም ለ5 ተከታታይ ቀናት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ የኬዝ አፃፃፍ ዘዴዎች እና ኬዞችን ተጠቅሞ ተማሪዎችን ማስተማርና መመዘን የሥልጠናው የትኩረት ነጥቦች ናቸው፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

16ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ‹‹ወንድማማችነት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል ኅዳር 29/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ