በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ (ዓባያ ካምፓስ) የተገነባው የአስተዳደርና የመምህራን ቢሮ ሕንፃ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንትና ሌሎች ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት ጥቅምት 26/2014 ዓ/ም ተመርቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለሳውላ ካምፓስ የአስተዳደር ሠራተኞች በሥርዓተ-ጾታና ጾታዊ ትንኮሳ ዙሪያ ጥቅምት 25/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የኅብረተሰቡን ችግር ሊፈቱ የሚችሉና በኢንደስትሪና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ ያተኮሩ 15 የምርምር ንድፈ ሃሳቦች ግምገማ ጥቅምት 30/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ከ “GIZ” ጋር በመተባበር ወጣቶችን በትምህርት ቤት በማሳተፍ በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ የመሬት መራቆትና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና የተራቆቱና የተጎዱ ሥነ-ምኅዳሮችን መልሶ ለማቋቋም በሚያስችል ፕሮጀክት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ጥቅምት 27/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ