የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የፎረንሲክ ሜዲስንና ቶክሲኮሎጂ ስፔሻሊቲ ተማሪዎች ከታኅሣሥ 18 - ጥር 24/2016 ዓ/ም በሁለት ዙሮች የፎረንሲክ ናሙና ምርመራ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ“Development Economics” ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ሰለሞን ከበደ  የካቲት 01/2016 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ  የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናው ግቢ መግቢያ ላይ በሚገኘው አዳራሽ ያቀርባል፡፡ 

የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት የባህሪ ማሻሻያ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከ“International Youth Fellowship” ጋር በመተባበር በአዕምሮ ውቅር (Mindset) ዙሪያ ከደቡብ ኮሪያ በመጡ አሠልጣኞች ለጫሞ ካምፓስና ለዋናው ግቢ 2 ዓመትና ከዚያ በላይ ተማሪዎች፣ ለመደበኛና ኢ-መደበኛ ሪሜዲያል ተማሪዎች እና ለባይራ አዳሪ 2ኛ ደ/ት/ቤት ተማሪዎች  ጥር 18/2016 ዓ/ም የአዕምሮ ውቅር/Mindset/ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርበ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ጋር በመተባበር ‹‹አርባ ምንጭ ታንብብ›› በሚል መሪ ቃል ከጥር 18-21/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ከተማ የንባብ ሳምንት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡