የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት ት/ክፍል ከአርባ ምንጭ መምህራን ማሠልጠኛ ትምህርት ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለኮሌጁ የአስተዳደር ሠራተኞች በየሥራ ጠባያቸው በመከፋፈል ከግንቦት 23-26/14 ዓ/ም በተቋማዊ ባህርይ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን አካባቢ ጥበቃና ልማት ጽ/ቤት፣ ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና ከGIZ-CLM /ጂ.አይ.ዘድ-ሲኤል.ኤም/ ጋር በመተባበር በዓለም ለ49ኛ በሀገራችን ለ29ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የአካባቢ ቀን ‹‹አንድ ምድር ብቻ! - ከተፈጥሮ ጋር በዘላቂነት ተስማምቶ መኖር!›› በሚል መሪ ቃል ግንቦት 27/2014 ዓ.ም አርባ ምንጭና አካባቢዋን በማጽዳት፣ ችግኝ በመትከልና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ በደማቅ ሁኔታ አክብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ሁዋዌ አይ.ሲ.ቲ አካዳሚ/Huawei ICT Academy/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ (ICT) እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬቶች ጋር በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪዎች ስለ ሁዋዌ አይ.ሲ.ቲ ታለንት ኢኮሲስተም /ICT Talent Ecosystem/ ግንቦት 24/2014 ዓ.ም ገለጻ/ ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

‹‹የምኅንድስናና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ለዘላቂ ልማት እና ተግዳሮቶች/3rd National Conference on Innovation and Challenges in Engineering and Technology for Sustainable Development›› በሚል ርዕስ 3ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ዓውደ ጥናት ከግንቦት 26 - 27/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ከፌዴራል፣ ከክልልና ከዞኑ ከመጡ ባለድርሻ ተቋማት አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እና ተመራማሪዎች ጋር ዘላቂ የትብብር ግንኙነት ሥራዎችን አብሮ መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ የጋራ ውይይት በቱሪስት ሆቴል ግንቦት 25/2014 ዓ.ም ተደርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ