የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት አባላትና አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ካምፓሶች እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ሥራዎች ያሉበትን ሁኔታ ሐምሌ 10/2012 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝደንት ወ/ሮ ታሪኳ ወ/መድኅን ጉብኝቱ በዩኒቨርሲቲ በካፒታል በጀት እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ የግንባታ ፕሮጀክቶች ያሉበትን የአፈፃፀም ደረጃና ተግዳሮቶች በአካል በማየት ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫና ውሳኔ ለመስጠት የሚረዱ ሀሳቦች ለማግኘት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ መሰል ጉብኝቶች ለዘርፉ ያላቸው ፋይዳ ጉልህ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ታሪኳ በዩኒቨርሲቲው ተጀምረው የቆዩ በዋናው ግቢና ዓባያ ካምፓስ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ከኮንትራክተሮቹ ጋር የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን እንዲሁም ሌሎች ስትራቴጂዎች ተቀይሰው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና ሕክምና  የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሐምሌ 9/2012 ዓ/ም ድጋፍ አድርጓል፡፡

በዕለቱ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በሆስፒታሉ ተገኝተው የተቋሙን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይ ዩኒቨርሲቲውና ሆስፒታሉ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ከስምምነት ደርሰዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

በዩኒቨርሲቲው የተዘነጉ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ተላላፊና ተላላፊ ባልሆነ በተለምዶ ‹‹ዝሆኔ›› ተብሎ በሚጠራው በሽታ መከላከልና ሕክምና አሰጣጥ ዙሪያ ከደቡብ ክልል 20 ወረዳዎች ለተወጣጡ 200 የጤና ባለሙያዎች ሥልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ ሥልጠናው ለ3 ቀናት የሚቆይና በ6 ዙር የሚሰጥ ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከከተማው 3 ቀበሌያት ለተወጣጡና  ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 250 አባወራዎችና እማወራዎች ለ2ኛ ጊዜ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ሰኔ 3/2012 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

መርሃ ግብሩ በዋናው ግቢ የውሃና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች እንዲሁም በኢትዮ- ፊሸሪ ኮንዶሚኒየም የሚኖሩ መምህራን ከግንቦትና ሰኔ ወር ደምወዛቸው በማዋጣት ያከናወኑት ነው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

ውድና የተከበራችሁ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ መምህራንና ተመራማሪዎች፣ አመራር አካላት፣የአስተዳደር ሠራተኞችና የቴክኒክ ባለሙያዎች በሙሉ
የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሶ የመጀመሪያዉ ዙር የዉሃ ሙሌት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ ያለን !!!