አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለጎፋ ዞን አስተዳደር የዞኑና የከተማው አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የአካባቢው ማኅበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የኮሮናቫይረስን ለመከላከልና ለማከም የሚውሉ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ግንቦት 5/2012 ዓ/ም አበርክቷል፡፡

የተደረገው ድጋፍ ለሳኒታይዘር ዝግጅት የሚውል 500 ሊትር አልኮል፣ 5 የሙቀት መለኪያዎች፣ ሰርጂካል የፊት መሸፈኛ ጭንብሎችና የእጅ ጓንቶች እንዲሁም ሌሎች የቫይረሱን ተጠቂዎች ለማከም የሚረዱ መድኃኒቶች ያካተተ መሆኑን የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺይፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምሩ ሽብሩ ገልፀዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና ሐኪሞች አማካኝነት በጎፋ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች ለተወጣጡ 60 የህክምና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል፣ ቁጥጥርና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 4-5/2012 ዓ/ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የቆየ ሥልጠና በሳውላ ከተማ ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

While COVID-19 continues to spread the trail of catastrophe all across that has literally halted the wheels of economic activities leaving many without monetary and other resources at this critical time, in such situation, AMU’s Community Service Directorate is assuaging the sufferings of poor, homeless and elders in Gamo Zone by distributing some public protection gears, cereals, other eatables, etc. in its own way.

ባሉበት

ውድ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ፣ ለመላዉ ዓለምም  ሆነ ለሀገራችን ሰው ልጅ ሁሉ በሕይወት ለመኖር እጅግ ከፍተኛ ስጋት ያመጣዉ የኮቭድ-19 መከሰት ምክንያት ለሕዝብና ለሀገር ደህንነት ታስቦ በትኩረት እየተሠራ ካለዉ አንጻር በሀገራችን የሁሉም ትምህርት ደረጃ ተማሪዎች  ወላጅ ወይም ቤተሰብ ዘንድ እንዲቆዩ በተደረገዉ ሂደት ከመጋቢት 19 እስከ 21/2012 ባሉት ቀናት ከዩኒቨርሲቲዉ  ግቢ ወጥታችሁ ወደየቤተሰቦቻችሁ ዘንድ ከሄዳችሁበት ቀን ጀምሮ እንደምን አላችሁ?  ውድ ተማሪዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ  6ቱም ግቢዎች የሚሞቁትና የሚያምሩት እናንተ ስትኖሩበትና በግቢያችሁ ወዲያ ወዲህ (ከዶርም ወደ ክፍል፣ ከክፍል፣ ወደ ላይብራሪና ማጥኛ ቦታዎች፣ ወደ ሻይ/ቡና ወይም መዝናኛ ቦታዎች፣ ወደ አቢያተክርስቲያናትና መስጂዶች ከዚያም ወደ ግቢ፣ ወደ ከተማና ከዚያም ወደ ግቢያችሁ) ሽርጉድ እያላችሁ ስትመላለሱ ብቻ ነዉ፡፡ በክረምት ዕረፍት ለሁለት ወራት ወደ ቤተሰብ ስትሄዱ የክረምት ተማሪዎች ይተኩ ነበር፡፡ አሁን ግን  ማንም ተማሪ የለም፡፡ የትምህርት ቤት/ተቋም ትልቁ የውበት ምንጭና ሕይወት ተማሪ ነዉ፡፡

In order to complement the ongoing global efforts to study and understand the catastrophic implications of COVID-19, Arba Minch University acting on the directive of Ministry of Science and Higher Education has constituted a Research Council that will soon launch specific research projects to study broader aspects that were left totally upended in the wake of Corona virus outbreak in recent times.