የ45 ቀን ዕድሜ ያላቸው 2,000 ሳሶ ብሮይለር ብሪድ/Saso Broiler Breed/ ዝርያ ጫጩቶችን በመረከብ ሥራ የጀመረው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንስሳትና ዓሣ ሀብት ምርምር ማእከል ከሚያዝያ 24/2015 ዓ/ም ጀምሮ 1,800 የእርድና እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ለሽያጭ አቅርቦ እየሸጠ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ ሚያዝያ 30/2015 ዓ/ም ባካሄደው ጉባዔ ወ/ሮ ታሪኳ ወ/መድኅን የዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝደንትና የአስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ተወካይ ሆነው ሲያገለግሉ በቆዩበት ጊዜ ያከናወኑት የሥራ አፈጻጸም በዩኒቨርሲቲው ቦርድና ሴኔት በጣም ጥሩ ሆኖ በመገምገሙ ወ/ሮ ታሪኳ በምክትል ፕሬዝደንት ኃላፊነት የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው ለሁለተኛ ዙር እንዲቀጥሉ ወስኗል፡፡

በወባ በሽታ መከላከልና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እየሠራ በሚገኘው “AMU-SENUPH II” ፕሮጀክት የወባ በሽታን ለመከላከል በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያና ምዕራብ ዓባያ ወረዳዎች በተመረጡ ቀበሌዎች ቤቶችን በማሻሻል እና የአይቨርሜክቲን (Ivermechtin) የከብት ህክምና (House Screening and Ivermechtin Cattle Treatment) በወባ ስርጭት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመረዳት የመስክ ትግበራ ለመጀመር የሚያስችል ውይይት ከባለድርሻዎች ጋር ሚያዝያ 18/2015 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ በተለያዩ ተቋማዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ጋር ሚያዝያ 30/2015 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡