የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ1ኛ ዓመት ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ ኮሌጁን መርጠው አዲስ ለተቀላቀሉ የ2 ዓመት ተማሪዎች የእንኳን ደኅና መጣችሁ አቀባበል እንዲሁም በ2014 ዓ/ም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የ 3 እና የ4 ዓመት ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ት/ክፍል በእንስሳት ስነ-ምግብ ‹‹Animal Nutrition›› ትምህርት ፕሮግራም ላለፉት 6 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ጌታቸው አብርሃም የምርምር ሥራውን መጋቢት 28/2015 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቦ ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት መስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ በጫልቆ ወንዝ ላይ የሚገነባውን የጫልቆ ግድብና መካከለኛ የመስኖ ጥናትና ዲዛይን ንድፍ ሪፖርት ግምገማ ከመጋቢት 26 - 27/2015 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Arba Minch University-Inter University Cooperation Program Project I organized four day training on Research and Dissemination Skills for AMU academic and research staff, PhD candidates, and the staff from Arba Minch College of Teachers’ Education and Arba Minch College of Health Sciences from April 4-7, 2023. Click here to see more pictures.