የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታዳሽ ኃይል ምርምር ማእከል በእንግሊዝ ሀገር ከሚገኙት "Crop Health and Protection /CHAP/" እና "Space and Water Solutions Ltd/LENKE/ "የተሰኙ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ‹‹Optimizing Energy Demand in Rural Communities via Precision Agriculture Technology/SWIFT/›› የተሰኘ አዲስ የትብብር ፕሮጀክት በጋርዳ ማርታ ወረዳ ሚያዝያ 18/2015 ዓ/ም ይፋ አድርጓል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሚያዝያ 12/2015 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ "Jhpiego" ጃፓይጎ ከተሰኘ መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትብብር እየሠራ ሲሆን በትብብር ሥራው የእስከ አሁን አፈፃፀምና ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን በተመለከተ ሚያዝያ 23/2015 ዓ/ም በአካዳሚክ ጉ/ም/ፕ/ጽ/ቤት ምክክር ተደርጓል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch University-Inter-University Cooperation Program Project III (P3) has conducted research dissemination and gap identification workshop on maternal and child health on April 19, 2023. Click here to see more pictures.

የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና አሠጣጥ እና የሪሜዲያል ተማሪዎች የማስተማር ሂደትን አስመልክቶ የተከናወኑ ተግባራት ያሉበት ሁኔታ እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ዲኖች፣ ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች፣ ከየትምህርት ክፍሉ የተወጣጡ ተማሪዎችና የተማሪዎች ኅብረት ተወካዮች በተገኙበት ግምገማዊ የውይይት መድረክ ሚያዝያ 11/2015 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡