በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ሥልጠናና ምርምር ማዕከል ከጤና ሚኒስቴርና ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር በመተባበር በተዘነጉ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ሀገር አቀፍ ፕሮግራም የመረጃ ጥራት ምዘና ጥናት ለማድረግ በተደረሰ ስምምነት መሠረት በመረጃ ሰብሳቢነት ለተመረጡ የኮሌጁ መምህራን ጥር 16/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የዩኒቨርሲቲውን የ2015 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ጥር 12/2015 ዓ/ም ገምግሟል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደበበ ኃይለገብርኤል የሕግ ቢሮ ጋር በመተባበር «የብሔር ፌዴራሊዝም ለኢትዮጵያ የተሻለ አማራጭ ነው ወይስ ስጋት?» እንዲሁም «በፖለቲካና በኢኮኖሚ የመልካም አስተዳደር ስኬትን ለማረጋገጥ የራስን ዕድል በራስ መወሰን ትክክለኛ አማራጭ ነው ወይስ አይደለም?» በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ጥር 14/2015 ዓ/ም የክርክር መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ከጀርመን ልማት ባንክ በተገኘ 25 ሚሊየን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ የጫሞ ሐይቅ ተፋሰስን ወደነበረበት ለመመለስ በቅርቡ ሥራ የሚጀምረው ፕሮጀክት ስኬታማ እንዲሆን ከጋሞና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ከደራሼ፣ ቡርጂና አማሮ ልዩ ወረዳዎች የተወጣጡ አስተዳዳሪዎችን እና የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ኃላፊዎችን ያካተተ የአመራሮች የጋራ መድረክ ጥር 10/2015 ዓ/ም በይፋ ተመሥርቷል፡፡ በዕለቱ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዘውዴም የአመራር መድረኩ ሰብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ሰብሳቢ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር እያሱ ኤሊያስ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ተመራማሪዎች ጋር በተለያዩ የምርምር ግኝቶች፣ ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችና በትብብር መሥራት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ዙሪያ ጥር 10/2015 ውይይት አካሂደዋል፡፡ ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡