ከየካቲት 6-8/2015 ዓ.ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጄዲሲ ኢትዮጵያ (JDC Ethiopia) ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በተፈጥሮ የጀርባ ጉብጠት (kyphosis)፣ ዝንፈት (Scoliosis) እና ጥመት ላለባቸው ታማሚዎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት ስለሚሰጥ አርባ ምንጭ እና አካባቢው የምትገኙና ሕክምናውን የምትፈልጉ ታማሚዎች የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ያሳውቃል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ እና የምርምር ዳይሬክቶሬቶች በመተባበር ለጀማሪ ሴት መምህራን ‹‹Basic of Research, Statistical Tools for Data Analysis and Interpretation, Manuscript Writing and the Tricks of the Publishing›› በሚል ርዕስ የምርምር ክሂሎት ማዳበሪያ ሥልጠና ከጥር 23-24/2015 ዓ/ም ሰጥተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ውኃ አዘል መሬቶችና የተፈጥሮ ምንጮች ላይ ከሚሠራው ‹‹Ethio-Wetlands and Natural Resources›› ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የዓለም ውኃ አዘል መሬቶች (World Wetlands Day) ቀንን አስመልክቶ ጥር 25/2015 ዓ/ም የጋራ ውይይት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ኦቾሎ ቀበሌ በቁንጭር (ቦልቦ)በሽታ ላይ ያከናወነው ታላቅ የምርምር ፕሮጀክት ውጤት  ለማኀበረሰቡ አጋር ተቋማት የማስተዋወቂያ ወርክሾፕ ጥር 26/2015 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arab Minch University inked a Memorandum of Understanding with D.Y. Patil Agriculture and Technical University of Talsande, India. The 5-year pact was signed by AMU's Vice President for Research and Community Engagement, Behailu Merdekios (Associate Professor), and Vice Chancellor of DYP-ATU, Prof.K.Prathapan, on 1st February, 2023. Click here to see more pictures.