የጋሞ ዞን አስተዳደር አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በጋንታ ኦቾሌ ቀበሌ የሚገኘውን ሦስት ሄክታር የጫሞ ሐይቅ ረግረጋማ መሬት መልሶ እንዲለማ ለሌቶ ዓሣ አስጋሪዎች ማኅበር ጥር 22/2015 ዓ.ም በይፋ አስረክቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጨኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የስነሕንፃና ከተማ ፕላን ፋከልቲ ሕንድ ሀገር ከሚገኘው ሂንዱስታን የቴክኖሎጂና ሳይንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የምርምር ዓውደ ጥናት ከጥር 22-23/2015 ዓ/ም በበይነመረብ አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ1979 ዓ/ም ከተመሠረተ ጀምሮ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በውሃ ምኅንድስና ዘርፍ ቀዳሚ አድርጎ ሲያሠለጥን የቆየ ሲሆን ወደ ዩኒቨርሲቲነት ካደገበት ከ1996 ዓ/ም ጀምሮ በበርካታ የምኅንድስና፣ የጤና፣ የግብርና፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ የማኅበራዊ ሳይንስና ስነሰብ፣ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ እንዲሁም በሕግ እና በስነትምህርትና ስነባህሪ ዘርፎች ምሁራንን በማፍራት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch Institute of Technology and Hindustan Institute of Technology & Science have hosted 1st joint online research symposium on Research in Architecture and Planning from January 30th to 31st, 2023. Click here to see more photos.