የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከጋሞ፣ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞና ኮንሶ ዞኖች ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በመተባበር ከኮሌጆቹ ለተወጣጡ መምህራን ‹‹Advance Solid Work››፣ ‹‹Basic Solid Work›› እና ‹‹ArchiCAD›› በተሰኙ ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከታኅሣሥ 10-14/2015 ዓ/ም የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር ከዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ለተወጣጡ መርማሪ ፖሊሶች በፎረሲንክ ወንጀል ምርመራ ዘዴ እና የፎረንሲክ ማስረጃ ዝግጅት ዙሪያ ከታኅሣሥ 12-14/ 2015 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን ለሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ከታኅሣሥ 13-14/2015 ዓ/ም የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ9ኛ ጊዜ በተከበረው የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት ላይ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ወክላ የቀረበችው የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል 4ኛ ዓመት ተማሪ ሱመያ ፌቲ ባቀረበችው የቢዝነስ ሃሳብ 2ኛ በመውጣት ኅዳር 25/2015 ዓ/ም ከሥራና ክሂሎት ሚኒስቴር 260 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆናለች፡፡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲም የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ማእከል ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ31 በሀገራችን ለ30ጊዜ የሚከበረው የአካል ጉዳተኞች ቀን ከ6ቱም ካምፓስ ከመጡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ጋር ታኅሣሥ 9/2015 ዓ/ም ተከብሯል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡