በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ በሀገራችን ለ18ኛ ጊዜ የተከበረው ዓለም ዓቀፍ የፀረ-ሙስና  ቀን  በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ9ኛ ጊዜ ‹‹ሙስናን መታገል በተግባር!››  በሚል መሪ ቃል ከኅዳር 26-27/2015 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ በፕሮግራሙም የዩኒቨርሲቲውን ቅጥር ግቢ ከማጽዳት ጀምሮ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር፣ ዕለቱን አስመልክቶ የተለያዩ ሰነዶች፣ ግጥሞችና መነባንቦች ቀርበዋል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Training Course Announcement

Integrated Decision Support System (IDSS)

February 13-17, 2023, Arba Minch University, Arba Minch, Ethiopia

ከቀን 26/3/2015 ዓ/ም ጀምሮ  በዩኒቨርሲቲው  የመማር  ማስተማር  ሥራ  በተሟላ  ሁኔታ  እየተከናወነ አለመሆኑ ይታወቃል፡፡  በዚህም  ምክንያት የዓመቱ  የትምህርት ጊዜ እየባከነ በመሆኑ ጉዳዩን  አስመልክቶ በየደረጃው  ካሉ የዩኒቨርሲቲው አመራር አካላት ጋር በተደረጉ ውይይቶች በዩኒቨርሲቲው  የመማር ማስተማር ሥራው እየተከናወነ የመምህራን ጥያቄዎችን  ከሚመለከታቸው  አካላት  ጋር  በመሆን  ማስቀጠል  እንደሚቻል  ታምኖበታል፡፡  ስለሆነም ከ30/3/2015 ዓ/ም ጀምሮ  ሁሉም  በሥራ  ላይ  ያላችሁ  (በትምህርት ላይ ያልሆናችሁ)  መምህራን   በመደበኛ  ሥራችሁ  ላይ እንድትገኙ  ዩኒቨርሲቲው  ያሳስባል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራ ሂደት ላይ ለመወያየት በ01/4/2015 ዓ/ም ከጧቱ 02፡00 ሰዓት ጀምሮ በዋናው ግቢ አዲሱ ስብሰባ አዳራሽ እንድትገኙ ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት /UNIDO – United Nations Industrial Development Organization/ እና የኢትዮጵያ ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን /FSSC – Food Safety System Certification/ ድርጅቶች፣ ከተለያዩ ኢንስቲትዩቶችና ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ባለሙያዎች፣  እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የምርምር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተርና ተመራማሪዎች የሽፈራው /Moringa Nursery Site/ ነርሰሪ ሳይትን ኅዳር 22/2015 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡