ዓለም አቀፍ የነጭ ሪባን ቀን ‹‹ሴቷን አከብራለሁ! ጥቃቷንም እከላከላለሁ!›› በሚል መሪ ቃል ታኅሣሥ 7/2015 ዓ/ም በሳውላ ካምፓስ ተከብሯል፡፡ በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ31ኛ በሀገራች ለ17ኛ ጊዜ ሲከበር ቆይቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ  ምንጭ ዩኒቨርሲቲን  ለ2ኛ ዙር በፕሬዝደንትነት ለማገልገል በመሾሜ ከፍ ያለ ደስታ የተሰማኝ መሆኑን በታላቅ አከብሮት እየገለጽኩኝ ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢውና ለሀገራችን ዕድገት ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተልዕኮዎች አኳያ  የሚጠበቅበትን በላቀ ደረጃ እንዲያበረክት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን ደረጃና ዝና ከፍ ለማድረግ ሁላችንም ተቀናጅተንና ተባብረን እንሥራ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ላለፉት ዓመታት በፕሬዝደንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የመጀመሪያ ዙር የሹመት ዘመን መጠናቀቅን ተከትሎ 13 ተፎካካሪዎች የተሳተፉበት ይፋዊ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ተካሂዶ በድጋሚ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ጾታዊ ጥቃትንና ትንኮሳን መከላከል በሚቻልበት መንገድ ላይ ከዋናው ግቢና ከተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ የሴት ተማሪዎች ኅብረት አደረጃጀቶች ጋር ከኅዳር 30-ታኅሣሥ 01/2015 ዓ/ም በየካምፓሶቻቸው ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹GIZ››፣ እፉዬ ገላ ኢቨንት ቴክኖሎጂና ኮንሰልተንሲ እና ኢትዮጆብስ ጋር በመተባበር ከኅዳር 22-26/2015 ዓ/ም በጫሞ ሐይቅ ዙሪያ ሀካቶን አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ