- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሠላም፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆን ከወዲሁ ይመኛል፡፡
መልካም በዓል!
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ከምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በእንቦጭ አረምና በአኩሪ አተር ጠቀሜታ ዙሪያ ከኢንዶኔዥያ በመጡ የመስኩ ባለሙያዎች ለኮሌጁ መምህራንና ተመራማሪዎች መስከረም 12/2015 ዓ/ም የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በእንቦጭ አረምና በአኩሪ አተር ጥቅሞች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቤልጂየም ሀገር 5 ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር የሚሠራው “AMU-IUC – Arba Minch University – Institutional University Cooperation” ፕሮግራም 2ኛ ዙር የኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሠ ጫፎና በኢትዮጵያ የቤልጂየም አምባሳደር ስቴፋን ቲጂስ/Stefaan Thijis/ በተገኙበት መስከረም 11/2015 ዓ/ም በይፋ ተጀምሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
አቶ ሙሉነህ መንገሻ ከአባታቸው ከአቶ መንገሻ ቃንኤ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዓለሚቱ በላቸው በቀድሞ በሰሜን ኦሞ ዞን በጋሞ አውራጃ በቁጫ ወረዳ መስከረም 12/1958 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞ በጎፋ ወረዳ በገልጣ ከተማ 1ኛ- 6ኛ ክፍል በገሪማ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ከ7ኛ- 8ኛ ክፍል በአርባ ምንጭ ከተማ በኩልፎ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እና ከ9ኛ- 10ኛ ክፍል የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አጠናቀዋል፡፡