- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት በ2016 የትምህርት ዘመን በመደበኛ፣ በማታ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ-ግብሮች መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 27 ቀን 2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት በኩል በአካል እንዲሁም በመረጃ መረብ https://forms.gle/vG9KfojLfCXkgZYU9 በኩል ምዝገባ መፈጸሙ ይታወቃል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ ̋Biotechnology” ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ሳምሶን ትዕዛዙ የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ማጠናቀቂያ የምርምር ሥራውን መስከረም 4/2016 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የስኬት ይሁንላችሁ፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ"Biodiversity Conservation and Management" ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ማቲዎስ አጊዜ የምርምር ሥራውን ነሐሴ 29/2015 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የፌዴራል ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለሥልጣን የፌዴራል የመንግሥት ተቋማትን የግዥ ሥርዓት ለማሻሻልና ለማዘመን በ“Electronic Government Procurement /eGP” ዙሪያ ለዘርፉ የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቲዎሪና በተግባር የተደገፈ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ከጳጉሜ 2-4 /2015 ዓ.ም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡