የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል የደረጃ ዶት ኮም እህት ኩባንያ/Dereja.Com Sister Company/ ከሆነው ኢንፎማይንድ ሶሉሽንስ “Infomind Solutions” እና ከጋሞ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ጋር በመተባበር ከአርባ ምንጭ ከተማ እና ከጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ ለተመረቁ ወጣቶች በ “Dereja Academy Accelerator Program”̋ ክሂሎት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ከነሐሴ 26/2015 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ወራት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch University has offered the British Council-funded hybrid training of trainers on Instructional English for Secondary School Teachers and Project Proposal Writing for Grants for Instructors of English Language and Literature, Ph.D. candidates, and Masters Students in the field, from October 2-3, 2023. Click here to see more photos.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለድኅረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዘገባችሁ እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በገለጸው መሠረት ለድኅረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (GAT) ያልተመዘገባችሁና የልምምድ ፈተናውን (Mock Exam) ያልወሰዳችሁ አመልካቾች የምዝገባና የልምምድ ፈተና መውሰጃ የመጨረሻ ቀን ነገ መስከረም 25/2016 ዓ/ም ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ ዕድሉን እንድትጠቀሙበት ዩኒቨርሲቲው እያሳሰበ ለመመዝገብ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴሌ ብር ሱፐርአፕ https://portal.aau.edu.et ወይም ለዚህ ፈተና ብቻ በሚያገለግለው https://gat.aau.edu.et  መጠቀም የምትችሉ መሆኑን ይገልጻል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የሥራ ባልደረባ የነበሩት ኢንጂነር ፍቃዱ ፈጠነ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከቀድሞ አርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከአሁኑ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሀይድሮሊክ ምኅንድስና ሐምሌ 5/1995 ዓ/ም እና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሀይድሮሊክና ፓወር ኢንጂነርንግ ኅዳር 10/2001 ዓ/ም አግኝተዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ትምህርት ክፍል በእንስሳት ሥነ-ምግብ/Animal Nutrition/ ትምህርት ፕሮግራም የ3ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ከበደ ገልገሎ የምርምር ሥራውን መስከረም 15/2016 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት አቅርቦ ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡