የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ፣ ግብርና ሳይንስ እና ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች በመተባበር 10ውን ሳይንስ ለዘላቂ ልማት ዐውደ ጥናት መጋቢት 21/2016 ዓ/ም አካሂደዋል፡፡ በዐውደ ጥናቱ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን 18 ጥናታዊ ጽሑፎችም ቀርበዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን በሚገኙ የተመረጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሳይንስ ቤተ ሙከራዎች ውስጥ ያሉ ኬሚካሎችንና ቁሳቁሶችን የመለየት፣ አስተማማኝ የሳይንስ ቤተ ሙከራዎችን አያያዝ መተግበርና መልሶ የማደራጀት ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር መጋቢት 16/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል ከደረጃ ዶት ኮምና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባባር ‹‹Arba Minch Job Fair›› በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የሥራ ዐውደ ርእይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 14/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከኢፌዲሪ የከተማና መሠረት ልማት ሚኒስቴር የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር ሀገር አቀፍ የውኃ ዘርፍ የኮንስትራክሽን ሥራዎች የሰው ኃይልና የማሽነሪዎች ምርታማነት ኖርም (Standard Productivity Norm) ላይ በጋራ ለመሥራት መጋቢት 12/2016 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ