ዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶችና የአገልግሎት አሰጣጥ መስፈርቱን እንዲሁም አገልግሎቱ የሚሰጥበትን ቦታና ደንበኞች አገልግሎት ለማግኘት በቅድሚያ ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታ በዝርዝር ለተገልጋዮች ለማሳወቅ የዜጎች ቻርተር አዘጋጅቷል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ህክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ የተቋቋመው “የተዘነጉ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች የትብብር ምርምርና ሥልጠና  ማዕከልˮ /Collaborative Research and Training Center for Neglected Tropical Diseases/ የሆድ ጥገኛ ትላትሎች እና ሺሽቶሶሚያሲስ/ቢልሃርዚያ/ በሽታ ህክምና ውጤታማነትን የሚፈትሽ ጥናት አካሂዷል፡፡

የተማሪዎች አገልግሎት ማዕከል ከአ/ምንጭ ተሀድሶ ማዕከል ጋር በመተባበር “አካል ጉዳተኛን ማካተት ወሳኝ ነው፤ ተደራሽነትና ማብቃት ለሁሉምˮ በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፉን የአካል ጉዳተኞች ቀን በ21/04/08 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው አክብሯል፡፡

Arba Minch University all set to launch its maiden three journals in Science, Water Science & Technology and Business & Social Science streams, in a daylong meeting at Main Campus recently, discussed all aspects of publications, technicalities and administrative parameters.

Grand Kulfo Watershed Project’s core team in a meeting evaluated the progress being made by all five committees in their respective realms. President, Dr Feleke Woldeyes, at the helm, while taking non-performing team to task asked others to scale up the efforts.