በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለተመራቂ ተማሪዎች የፊታችን ሐሙስ መስከረም 05/2015 ዓ/ም ከቀኑ 08፡00 – 11፡30 በኩልፎ ካምፓስ፣ ዓርብ መስከረም 6/2015 ዓ.ም ከጧቱ 2፡00 – 06፡30 በቴክኖሎጂና በውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች እና ከሰዓት ከ08፡00 – 11፡30 በዓባያ ካምፓስ እንዲሁም ሰኞ መስከረም 9/2015 ዓ/ም ከጧቱ 2፡00 – 06፡30 በነጭ ሳር ካምፓስ በሥነ-ምግባርና ሞራል ዕሴቶች ግንባታ እና ብልሹ አሠራርን በመከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማዳበሪያ ሥልጠና በዋናው ግቢ በቴክኖሎጂ ትልቁ አዳራሽ እና በካምፓሶች በተማሪዎች መመገቢያ አዳራሾች የሚሰጥ ስለሆነ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ በመገኘት ሥልጠናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን፡፡

Arba Minch University expresses heart-felt condolences on the death of Radhakrishnan Duraisamy (PhD), Arba Minch Water Technology Institute expat staff, on 28/08/2022, in India.

Dr Radhakrishnan was serving in the Faculty of Water Resource and Irrigation Engineering since Nov. 2019. He was married and had children. He was a kind and courageous person with strong desire and appreciation for knowledge and self-development.

የአርባ ምንጭ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ አዲሱን 2015 ዓ/ም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ 2014 ዓ/ም በመማር ማስተማር፣ በምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት እና ሌሎችም ሀገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች በተሻለ ሁኔታ ተከናውነው የተጠናቀቁበት፣ በርካታ የመጀመሪያ፣ 2ና 3 ዲግሪ ተማሪዎች የተመረቁበት ሲሆን ከዚህ አንፃር የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ለተቋሙና ለሀገር ያደረገው አስተዋጽኦ እንዲሁም ለስኬቶቹ  የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ሚና ከፍ ያለ በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ምስጋናና አድናቆት አቅርበዋል፡፡

ፕሬዝደንቱ አዲሱ 2015 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲያችን፣ ለሌሎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የትምህርት ማኅበረሰብ እንዲሁም ለሀገራችን ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነት፣ የእድገትና የብልጽግና ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲሱን ዓመት በማስመልከት ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞች፣ በተለያዩ  ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡና ለዘማች ቤተሰብ አባላት በድምሩ ለ115 አባወራዎች ለእያንዳንዳቸው 25 ኪሎ ግራም በድምሩ 29 ኩንታል የሚሆን የፉርኖ ዱቄት ለማዕድ ማጋራት እንዲውል ለአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 03/2014 ዓ/ም አስረክቧል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን 150 ሺ ብር የሚጠጋ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ