የዩኒቨርሲቲው የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ የእንስሳት መኖ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እና የአፈር ለምነትን መጠበቅ ላይ የሚሠራ የምርምር ሜጋ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ታኅሣሥ 09/2016 ዓ/ም በገረሴ ከተማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Embassy of Canada in Ethiopia in collaboration with Arba Minch University hosted a day-long informative session on higher education opportunities in Canada for AMU academic staff and students on December 12, 2023. Click here to see more photos.

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር በኅብረተሰብ ጤና ትምህርት የ2 ዲግሪ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች የልማታዊ ቡድን ሥልጠና ፕሮግራምን/Developmental Team Training Program /DTTP/ መሠረት በማድረግ በአርባ ምንጭ ከተማ ጉርባ ቀበሌ የአካባቢውን ማኅበረሰብና አጋር አካላትን በማስተባበር ያስገነቡት የደረቅ ቆሻሻ መጣያና ከጤና ተቋማት የሚወጡ የሕክምና ዕቃዎች ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator) ታኅሣሥ 06/2016 ዓ/ም ተመርቆ ለማኅበረሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በኮንትራት ውል መሠረት በደብዳቤ የተስተናገዳችሁ የቀድሞ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2ና 3 ዲግሪ ተመራቂዎች የቀድሞ ደብዳቤ ወደ ሰርተፊኬት እንዲቀየርላችሁ የቀረበ ጥያቄ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል ውሳኔ ማግኘቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሠረት የምረቃ ደብዳቤው ወደ ሰርተፊኬት እንዲቀይርላችሁ የምትፈልጉ በሙሉ በእጃችሁ የሚገኘውን የቀድሞ ደብዳቤ ኮፒ በመመለስ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃ (Temporary Certificate of Graduation) ከሰኞ ታኅሣሥ 15/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ወቅታዊውን የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ አስመልክቶ ‹‹የባሕር በር የልማት በር›› በሚል ርእስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ታኅሣሥ 12/2016 ዓ/ም የፓናል ውይይት አዘጋጅቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡