Arba Minch University marks 4th Doctoral day and welcomes newly graduated PhD staff from different Universities on 1st April, 2023. Click here to see Pictures.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ካሉ አንጋፋና ስመ ጥር ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንን መልካም ስም በገበያ አማራጭነት ለመጠቀም ያሰቡ አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የዩኒቨርሲቲው ያልሆኑ የትምህርት ማስረጃዎች እና የተማሪ ውጤት ኮፒዎች ላይ የዩኒቨርሲቲውን ሎጎ ተጠቅመው የዩኒቨርሲቲውን ስም እያጎደፉ መሆኑን ከተለያዩ ተቋማት ከሚቀርቡ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ጥያቄዎች ለመረዳት ተችሏል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ት/ክፍል በእንስሳት ስነ-ምግብ ‹‹Animal Nutrition›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ዕጩ ዶ/ር ጌታቸው አብርሃም መጋቢት 28/2015 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ የ3ኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፋቸውን የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት በዋናው ግቢ አዲሱ አዳራሽ ያቀርባሉ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ-ምግባርና ፀ/ሙ/መከ/ዳይሬክቶሬት ቅዳሜ መጋቢት 23/2015 ዓ.ም ጧት ከ2፡00 ሰዓት ጀምሮ አዲስ ገቢ ተማሪዎች የመጡበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በትምህርት ቆይታቸው ሊተገብሩ የሚገባቸውን የሥነ-ምግባር መርሆዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ዲሲፕሊን መመሪያን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና አዘጋጅቷል፡፡