Ethiopian Journal of Water Science & Technology of Arba Minch University got accredited by Federal Ministry of Education for the next three years.

Congratulations to AMU and all well-wishers!

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ማዕከል ጋር በመተባበር መጋቢት 19/2015 ዓ/ም ‹‹የኢንተርኔት መገደብ ተገቢ ነው ወይስ አይደለም?›› በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ በተማሪዎች መካከል የክርክር መድረክ አካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ በዝናብ እጥረት ምክንያት ለድርቅ ለተጋለጡና አስቸኳይ የምግብ እህል ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች 70 ኩንታል የምግብ በቆሎ መጋቢት 18/2015 ዓ/ም በካምባ ከተማ ተገኝቶ አስረክቧል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከአራቱም ፋከልቲዎች ከተወጣጡ የ2015 ዓ/ም የኢንስቲትዩቱ ተመራቂ ተማሪዎች ተወካዮች ጋር የመውጫ ፈተና ቅድመ ዝግጀትን በተመለከተ መጋቢት 15/2015 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ማዕከል ማስ/ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማው ከሚገኙ ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በአዲሱ የኤች አይ ቪ/HIV/ ፈጣን ምርመራ አልጎሪዝም ዙሪያ ከመጋቢት 16-18/2015 ዓ/ም ድረስ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡