- Details
ወ/ሮ እታገኝ ጓሉ ከአባታቸው ከአቶ ጓሉ ገብሬ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወጋየሁ ጓሉ በቀድሞ ወሎ ክፍለ ሀገር በወልድያ ከተማ የካቲት 16/1974 ዓ/ም ተወለዱ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹የምሁራን ሚና ለሀገራዊ መግባባት›› በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የሥራ ኃላፊዎችና ተማሪዎች በተገኙበት የካቲት 25/2015 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል በደቡብ ኦሞ ዞን በተለይም በሙርሲ አካባቢ የቪሰራል ሌሽማኒያሲስ/Visceral Leishmaniasis/ በሽታ ተጠቂዎች ቁጥር ማሻቀብን ተከትሎ የምርመራ ናሙና ለሚወስዱ ሐኪሞችና ወረርሽን መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ ዳሰሳ ለሚያካሂዱ ከዞኑ ወረዳዎችና ከጂንካ ከተማ ለተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የካቲት 25/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በቪሰራል ሌሽማኒያሲስVisceral Leishmaniasis ዙሪያ የምርመራ ናሙና አወሳሰድና የወረርሽኝ ዳሰሳ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
127ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ‹‹ዝክረ ዓድዋ ድል ለብሔራዊ መግባባት›› በሚል መሪ ቃል ያለፈውን ታሪክ በመዘከር፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጸና እና የሀገር ግንባታን በሚያጠናክር መንፈስ የካቲት 23/2015 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial Program/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉትን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግል ከፍሎ ለመማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡