በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በባዮቴክኖሎጂ ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ብርሃኑ ገመዳ መጋቢት 22/2015 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዓባያ ካምፓስ በአዲሱ አስተዳደር ሕንፃ አዳራሽ ያቀርባል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝ (Autonomous) አስተዳደር ራሱን ለማስተዳደር እያከናወነ ባለው እንቅስቃሴና ተቋሙ በሚገኝበት አሁናዊ ደረጃ ዙሪያ ከፍተኛ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በተገኙበት ከዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት ጋር መጋቢት 8/2015 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ::

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለጫሞ ካምፓስ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበልና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የ3እና 4 ዓመት ሴት ተማሪዎች የማበረታቻ መርሃ ግብር መጋቢት 7/2015 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድ/ማስ/ጽ/ቤት በሸክላ ሥራና በእንጨት ለቀማ የሚተዳደሩ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ገቢ በማሳደግ አኗኗር ማሻሻል የሚያስችሉ ሁለት ግራንድ ፕሮጀክቶችን ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መጋቢት 8/2015 ዓ/ም በይፋ ሥራ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ምርምር ማእከል ሳሶ ብሮይለር ብሪድ/Saso Broiler Breed/ ዝርያ ያላቸው ሁለት ሺህ ጫጩቶችን በግዥ በማስመጣት ያስጀመረው የዶሮ እርባታ ጣቢያ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እና የማእከሉ ተመራማሪዎች በተገኙበት መጋቢት 7/2015 ዓ/ም ተጎብኝቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ